Amharic Gospel Literature
የአንተ ወዳጅ
ኢየሱስ የአንተ ወዳጅ
እኔ አንድ ወዳጅ አለኝ፡፡ እርሱ ከወዳጆቼ ሁሉ ይልቅ የቅርብ ወዳጄ ነው፡፡ እርሱ በጣም ደግና እውነተኛ ስለሆነ አንተም እንድትተዋወቀው እፈልጋለሁ፡፡ ስሙ ኢየሱስ ይባላል፡፡ እርሱ የአንተም ወዳጅ መሆን ስለሚፈልግ በጣም ድንቅ ነገር ነው፡፡
ስለ እርሱ ልንገርህ፡፡ የእርሱን ታሪክ ከመጽሐፍ ቅዱስ እናነባለን፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እውነትና የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡
አለምና በአለም ውስጥ ያለውን ሁሉ የፈጠረ እግዚአብሔር ነው፡፡ እርሱ የሰማይና የምድር አምላክ ነው፡፡ እርሱ ሕይወትንና እስትንፋስን ለሁሉም ይሰጣል፡፡
ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው፡፡ ኢየሱስ የግል አዳኛችን እንዲሆን እግዚአብሔር ከሰማይ ላከው፡፡ እግዚአብሔር ዓለሙን በጣም ስለወደደ (ያ ማለት አንተንና እኔን ወደደ ማለት ነው) አንድያ ልጁ የሆነው ኢየሱስን ለኃጢአታችን እንዲሞትና የሚያምንበት ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ ወደ አለም ላከው (ዮሐንስ 3፥16)፡፡
ኢየሱስ ወደ ምድር እንደ ትንሽ ሕጻን ልጅ መጣ፡፡ በምድር ላይ በነበረበት ወቅት አባትና እናቱ ዮሴፍና ማርያም ነበሩ፡፡ እርሱ በጋጣ ተወልዶና በግርግም ተኝቶ ነበር፡፡
ኢየሱስ ከዮሴፍና ማርያም ጋር አድጓልና ታዘዛቸው፡፡ አብሯቸው የሚጫወታቸው ወንድሞችና እህቶች ነበሩት፡፡ ዮሴፍንም በአናጺነት ስራው ያግዘው ነበር፡፡
ኢየሱስ ትልቅ ሰው ሲሆን ሰዎችን ስለ ሰማይ አባቱ አስተማራቸው፡፡ እግዚአብሔር እንደሚወዳቸው አሳያቸው፡፡ ሕመምተኞችን ፈወሰ፤ በችግር ወስጥ የነበሩትንም ሁሉ አጽናና፡፡ ኢየሱስ የልጆች ወዳጅ ነበር፡፡ ልጆች ወደ እርሱ እንዲቀርቡ ፈለገ፡፡ ለእንርሱም ጊዜ ሰጣቸው፡፡ ልጆች ኢየሱስን ወደዱት፤ ከእርሱም ጋር አብረው ጊዜ ማሳለፍን ይወዱ ነበር፡፡
አንዳንድ ሰዎች ኢየሱስን አልወደዱትም፡፡ ተመቀኙትና ጠሉት፡፡ በጣም ስለጠሉትም ሊገድሉት ፈለጉ፡፡ አንድ አሰቃቂ ቀን ኢየሱስን በመስቀል ሰቅለው ገደሉት፡፡ ኢየሱስ ምንም በደል አልሰራም ነበር፡፡ አንተና እኔ ስለ በደልን እርሱ በቦታችን ሞተ፡፡
የኢየሱስ ታሪክ በሞቱ አያበቃም፡፡ እግዚአብሔር ከሞት አስነሳው! ተከታዮቹም አዩት፡፡ ከዛም አንድ ቀን ወደ ሰማይ ተመለሰ፡፡
ዛሬ እርሱ ሊያይህና ሊሰማህ ይችላል፡፡ እርሱ ስላንተ ሁሉን ያውቃል፤ ይጠብቅህማል፡፡ በጸሎት ወደ እርሱ ና፡፡
አድምጥ! የሚጠራህ ማን ነው?
የዮሐንስ ወንጌል 10፡ 1-18
አንድ ሰው ሲጠራህና የሚጠራህ ሰው ድምጽ ከየት አቅጣጫ እንደሚመጣ ለማወቅ ግራ ተጋብተህ ታውቅ ይሆን? ወይም ብዙ ጫጫታ መካከል ከመሆንህ የተነሳ የሚጠራህን ሰው ድምጽ ለመስማት ተቸግረህ ታውቅ ይሆን?
አድምጥ! አንድ ድምጽ እየጠራህ ነው፡፡ አዎ አንተን!
አንተ ማን ነህ? ስምህ ማን ነው? ከየት ነው የመጣኸው? የት ነው ምትኖረው? ወዴትስ እየተጓዝክ ነው?
የምትኖርበትን አካባቢ ስም ታውቃለህ፡፡ ድነገትም ከምትኖርበት አካባቢ ርቀህ ተጉዘህ አታውቅ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የምትኖርበት አካባቢ የአንድ አገር አካል፤ አገራት ደግሞ የአለም አካል እንደሆኑ ታውቃለህ;፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ
አለማችን ከተፈጠረች 6,000 ዓመታት ሆንዋታል፡፡ የተፈጠረችውም በእግዚአብሔር ነው፡፡ እግዚአብሔር ዓለምንና የመጀመሪያውን ሰው እንዴት እንደፈጠረ የተረከበት መጽሐፍ ቅዱስ የተባለ መጽሐፍ አለው፡፡ እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው በአምሳሉ ነው፡፡
ከዚያን ግዜ ጀምሮ ብዙ ልጆች ተወልደዋል፡፡ ብዙ ሰውችም ሞተዋል፡፡
አንተ የተወለድከው ከአባትና እናትህ ነው፡፡ ነገር ግን የሰራህ እግዚአብሔር ነው፡፡ እርሱ አንተን ብቻ ሳይሆን ሁሉን ነገር የፈጠረ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን ነገር እንዴት አድርጎ እንደ ሰራ እና አንተን እንዴት አድርጎ እንደፈጠረ አስበህ ታውቅ ይሆን?
ወላጆችህ ስም አውጥተውልሀል፡፡ እግዚአብሔር ስምህን ያውቃል፡፡ በማንኛውም ቋንቋ ቢሆን እግዚአብሔር የእያንዳንዱን ሰው ስም ያውቃል፡፡ እርሱ ሁሉን አዋቂ ነው፡፡
እግዚአብሔር ፈጣሪያችን ስለሆን ስለ እኛ ሁሉን ያውቃል፡፡ እኛ የእርሱ ስለሆንን ይወደናል፡፡ እርሱ ከአባትና እናታችን ይልቅ አብልጦ የሚጠነቀቅልን በሰማይ የሚኖር አባታችን ነው፡፡
እግዚአብሔር
እግዚአብሔር የነበረ፣ ያለ እና ለዘላለም የሚኖር አምላክ ነው፡፡ ስለዚህም እስትንፋሱን በሰጠን ጊዜ እኛንም ለዘላለም እንድንኖር አድርጎናል፡፡ ነገር ግን ስጋችን ሟች ስለሆነ እርሱ ሳይሆን ለዘላለም የሚኖረው በውስጣችን የምትኖር ነብሳችን ነች ዘላለማዊ፡፡
እግዚአብሔርን ታውቀዋለህ? ድንገት “እግዚአብሔር ማን ነው? የትስ ነው የሚኖረው?” ብለህ ትጠይቅ ይሆናል፡፡
በእርግጥ ማወቅ ትፈልጋለህ? አዎ! በርግጥም ማወቅ ትፈልጋለህ፡፡ ውስጥህ በርግጥም ማወቅ ይፈልጋል፡፡
እግዚአብሔርን አይተኸው አታውቅም፤ ታውቃለህ እንዴ? አላየኸውም ማለት እኮ ታዲያ እግዚአብሔር የለም ማለት አይደለም፡፡
አንድ እግዚአብሔር ብቻ ነው ያለው፡፡ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ምክንያቱም እውነተኛ አምላክ በሰማይና በምድር የሚኖር አምላክ ነው፡፡ እርሱ በአንድ ጊዜ በሁሉም ቦታ ይገኛል፡፡
የእግዚአብሔር መኖሪያ የተዋበውና በላይ ያለው ሰማይ ነው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ድምጹን በሚታዘዙ ሰዎች ልብም ውስጥ ይኖራል፡፡
“እግዚአብሔርን ለማወቅ እንዴት መማር እችላለሁ?” የሚለውን ጥያቄ ትጠይቅ ይሆን? እግዚአብሔር እንዴት ልናውቀው እንደምንችል ድንቅ መንገድን አዘጋጅቶልናል፡፡
እግዚአብሔር ማን እንደሆነ እና ምን እንደሚመስል ለሰዎች ሁሉ እንዲያሳይ አንድያ ልጁ የሆነውን ኢየሱስን ከሰማይ ልኮታል፡፡ አብና ወልድ አንድ ናቸው፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ በተአምራት ህጻን ልጅ ሆኖ ተወለደ፤ ትልቅም ሰው ሆኖ አደገ፡፡ ኢየሱስ ካደገ በኋላ ለሶስት ዓመታት ስለአባቱ ፍቅር ለሰዎች አስተማረ፡፡ ጨምሮም እግዚአብሔር ቅዱስ እንደሆነና ኃጢአትን እንደሚጸየፍ አስተማረ፡፡
ከዛም እግዚአብሔር ከኃጢአታችን የምንድንበትን መንገድ አዘጋጀልን፡፡ ልጁ ኢየሱስ በክፉዎች እጅ ወድቆ መስቀል ላይ እንዲሰቀል ፈቀደ፡፡ ኢየሱስ ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ ሕይወቱን ስለ እኛ አሳልፎ ሰጠ!
ኢየሱስ የዓለምን ሁሉ የኃጢአት ዋጋ ሊከፍል የቻለ መስዋዕት ነበር፡፡ አንተ ለሰራኸው ኃጢአት ሁሉ፤ ለትልቅ ለትንሹ፤ ለወንድ ለሴቱ ኃጢአት ሁሉ መስዋዕት የሆነው ኢየሱስ ነው፡፡
ኢየሱስ በመስቀል ላይ እንደተሰቀለ ቀረን? በመቃብርስ ተቀብሮ ቀረ? በፍጹም፣ ከሶስት ቀን በኋላ በድል ተነስቶ ወደ ሰማይ አረገ፡፡ የዚህች ዓለም ፍጻሜ በሚሆንበት ጊዜ የሰው ሁሉ ጻድቅ ፈራጅ ሆኖ ይገለጣል፡፡
የዮሐንስ ወንጌል ካለህ ምዕራፍ አስርን (10) አንብብ፡፡ ዮሐንስ ኢየሱስ ለህዝቡ ምን ያስተምራቸው እንደነበር ነው የጻፈው፡፡ ኢየሱስ ያን ጊዜ ለህዝቡ ያስተማረው ትምህር ዛሬ ለእኛም ትምህርት ነው፡፡ ኢየሱስ መልካም እረኛ እንደሆነ እና ነፍሱንም ስለ በጎቹ አሳልፎ እንደሰጠ ተናግርዋል፡፡ በጎቹ ደግሞ እኛ ነን፡፡ በጎቹ የሆኑት ድምጹን ያውቃሉ፡፡ እያንዳንዳቸውን በስም ይጠራቸዋል፤ እነሱም ሌላውን ከመከተል ይሸሻሉ፡፡
እንግዳው፤ ሌላኛው ድምጽ
እንግዳ የተባለው እና ልንሸሸው የሚገባው ማንን ነው? ኦ! ሌባውን ነው፡፡ እርሱ ስለ በጎቹ ምንም ደንታ የለውም፡፡ ውሸታም ስለሆነ አንዳች እውነት በእርሱ ዘንድ የለም፡፡ እርሱ ዲያብሎስ ነው፤ እርሱ ጠላታችን የሆነው ሰይጣን ነው፡፡
አስቀድሞ እርሱ የእግዚአብሔር ጠላት ነው፡፡ በአንድ ወቅት ከእግዚአብሔር ጋር በሰማይ ይኖር የነበረ ቅዱስ መልአክ ነበር፡፡ ነገር ግን በትዕቢት እራሱን ከእግዚአብሔር በላይ ከፍ ሊያደርግ ሞከረ፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር ተዋጋ፣ ብዙ መላእክትም ተባበሩት፡፡ እግዚአብሔር ኃያል ስለሆነ ድል በመንሳት ሰይጣንን ከነተከታዮቹ ከገነት አባረራቸው፡፡ ከዚህም የተነሳ ሰይጣንን እግዚአብሔርን ይጠላዋል፡፡
ሰይጣን እግዚአብሔር አጠገብ መቅረብ ስለማይችል እግዚአብሔር በአምሳሉ በፈጠራቸው ሰዎች ላይ ተቆጣ፡፡ ሰይጣን ኃጢአተኛ ስለሆነ ሰው ሁሉ ኃጢአት እንዲሰራ ያባብላል፡፡ ኃጢአት ዳግመኛ ወደ ገነት ሊገባ ፈጽሞ አይችልም፡፡
እግዚአብሔር ለዲያብሎስ እና መላእክቱ ሁሉ የሰራው ሌላ ስፍራ አለ፡፡ ይህ ስፍራ ሲኦል ነው፡፡ ሲኦል እሳቱ የማይጠፋ የስቃይ ቦታ ነው፡፡ ዲያብሎስ እና ተከታዮቹ ሁሉ ለዘላለም የሚቀጡበት ቦታ ነው፡፡ እኛም የሰይጣንን ድምጽ ለመስማት የምንመርጥ ከሆነ እግዚአብሔር ወደዚህ ቦታ ይልከናል፡፡
ሰይጣን ስለ ሲኦልም ሆን ስለ እግዚአብሔር እንድናስብ አይፈልግም፡፡ ስለ እግዚአብሔር እንድናስብ ስለማይፈልግ ስለ እግዚአብሔር የሆኑ ሀሳቦቻችንን ሁሉ በመስረቅ የእርሱን ድምጽ እንድንሰማ ሊያደርገን ይሞክራል፡፡
በውስጥህ ያን የተለየውን የእንግዳውን ድምጽ ሰምተህ ታውቃለህ?
ሰይጣን አንዳንዴ መልካም ነገር እንደሚሰጠን አድርጎ ያሳምነናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ “እኔ ከሌሎች የተሻልኩ ነኝ፤ እኔ ከማንም በላይ አስፈላጊ ሰው ነኝ፤ ቅድሚያ ለእኔ ነው የሚገባው፤ አለቀውም/አለቃትም፤ ለመብቴ መታገል አለብኝ፤ በቂ ስለማላገኝ ብሰርቅም ችግር የለውም፤ ሁሉ ስለሚዋሹ እኔም ብዋሽ ችግር የለውም፤ ምን እያሰብኩ እንደሆነ ማንም ስለማያውቅ ጸያፍ ሀሳቦችን ባስብ ምንም ችግር የለውም፤ በብልግና የተሞሉ ቃላት በጣም ስለሚያስቁ ምንም ችግር የለባቸውም” ብለን እንድናስብ ያደርገናል፡፡
በሌላ ጊዜ ደግሞ ተስፋ አስቆርጦን “የማልረባ ነኝ፤ በሕይወት መኖሬ ምንም ትርጉም የለውም” ብለን እንድናስብ ያደርጋል፡፡
እነዚህ ሁሉ የዲያብሎስ ድምጾች ናቸው፡፡ እርሱ ውሸታም ነው፤ እኛንም ውሸታሞች ሊያደርገን የሚጥረው ለዚህ ነው፡፡ እርሱ ሌባ ነው፤ እኛም እንድንሰርቅ የሚፈልገው ለዚህ ነው፡፡ እርሱ ነፍሰ ገዳይ ነው፤ እኛም ሌሎችን የምንጠላ ሰዎች ሊያደርገን የሚጥረው ለዚህ ነው፡፡
ይህንን አይነቱን ድምጽ ስትሰማ ምን ዓይነት ስሜት ይሰማሀል? ውስጥህን ደስ ያሰኝህ ይሆን? ኦ! በፍጹም ደስታ እንዳይሰማህ ያደርጋል፡፡ መደበቅ እንድትፈልግ ያደርግሀል፡፡ ሰይጣንም ልክ እንደዚህ ነው፤ ነገሮችን በጨለማ ተደብቆ ማድረግ ነው የሚወደው፡፡
ኢየሱስ፤ የእረኛው ድምጽ
መልካሙን እረኛ ኢየሱስን ታውቀዋለህን? የእርሱ በግ መሆን ትፈልጋለህን? ድምጹን ማወቅ ትፈልጋለህን?
አዎ ትችላለህ፡፡ ነገር ግን በመጀመሪያ ያንን ሌላኛውን ድምጽ መስማት ማቆም አለብህ፡፡
በጸጥታ ውስጥ ሆነህ ስታዳምጥ ኢየሱስ ዝግ ባለ ድምጽ ሕይወትህን አሳልፈህ እንድትሰጠው ጥሪን ሲያቀርብልህ ትሰማዋለህ፡፡ ኃጢአትህን ሁሉ ተናዘህ ንስሀ እንድትገባ ሲነግርህ ትሰማዋለህ፡፡
አንዳንድ ጊዜ ተረጋግተህ ተቀምጠህ ሳለ “ችግሮቼን እና ሸክሞቼን ምን ላድርጋቸው? መልካም ሰው ብሆን እመኛለሁ፤ የማልታመምበት ወይም የማልራብበት ቦታ ብኖር ማናለ፤ ስሞት ምን እሆናለሁ?” የሚሉ ሀሳቦች አስበህ ሊሆን ይችላል፡፡
ድንገት ከእነዚህ የበለጡ ብዙ ሀሳቦች አስበህ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ ድምጽ ኢየሱስ አንተን እየተጠራ ያለበት ድምጽ ነው፡፡
አንዳንድ ጊዜ ምክንያቱን ሳታውቀው የሀዘን ስሜት ይሰማህ ይሆን? ወይም ሰው አብሮህ እያለ የብቸኝነት ስሜት ይሰማህ ይሆን? ይህ የሚሆንበት ምክንያት የፈጠረህና ሚወድህ እግዚአብሔር አብሮህ ስላልሆነ ሊሆን ይችላል፡፡ እርሱ የጠፉትን በጎቹን የሚፈልግ እረኛ ነው፡፡ ደጋግሞ እየጠራህ እና እየፈለገህ ነው!
የእረኛውን ድምጽ ስትሰማ መልስን ስጠው፡፡ ከኃጢአትህ ነጻ መውጣት እንደምትፈልግ ንገረው፡፡ የሚሰማህን ንገረው፤ እንዲያድንህም ጠይቀው፡፡ ጸሎት ማለት እንደዚህ ነው፡፡
ወደ ሰማይ አምላክ እግዚአብሔር ጸልየህ ታውቅ ይሆን? አሁኑኑ ጸልይ፡፡ እርሱ ይሰማሀለ፤ ይረዳህማል፡፡ ዘወትር የምትናፍቀውን ሰላም ይሰጥሀል፡፡
የእርሱ በግ በመሆን ድምጹን ማወቅ ትፈልጋለህ? እርሱ ወዳጅህ ሊሆንህ እና ከኃጢአት ሸክምህ ሊያሳርፍህ ይፈልጋል፡፡ ያን ጊዜ ውስጥህ በደስታ ይሞላል፤ እንደ እርሱም አፍቃሪ እና ቸር ትሆናለህ፡፡ ፍራቻዎችህን ሁሉ ድል እንድትነሳ ይረዳሀል፡፡
ሌሎች ክርስቲያን በመሆንህ ቢያሾፉብህም አንተ ግን ኢየሱስ እንደሚጠነቀቅልህ ትረዳለህ፡፡ እንግዳው እየመጣ ቢፈትንህም ኢየሱስ እንድታሸንፈው እንደሚረዳህ ልታምነው ይገባል፡፡
በእረኛው የፍቅር እቅፍ ውስጥ ስታርፍ፣ እርሱ በመጨረሻ ድንቅ ወደ ሆነውና በደስታ ወደ ተሞላው ቤቱ ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም እንድትኖር እንደሚወስድህ ትረዳለህ
(ክፍሊቱ)
በእንቅልፍ ሰመመን ውስጥ ሆኜ እራሴን በአንዲት ክፍል ውስጥ አገኘሁት፡፡ በዚህች ክፍል ውስጥ አንደኛውን የክፍልዋን ግድግዳ ከሸፈነው ትንንሽ የስምና የአድራሻ ማውጫ አይነት ካርዶችን የያዙ ማህደሮች ከተደረደሩበት መደርደሪያ በስተቀር ምንም የተለየ ነገር አልነበረም፡፡ እነዚህ ማህደሮች በቤተ መጽሐፍት ውስጥ ደራሲን ወይም የመጽሐፍን ርዕስ ተጠቅመን መጽሐፍ እንደመናወጣባቸው ካርዶች በፊደል ቅደም ተከተል የተደረደሩ ነበር፡፡ እነዚህ ማህደሮች ከወለሉ አንስተው እስከ ጣራው ድረስ ተደርድረው በሁለቱም አቅጣጫ መጨረሻ የሌላቸው ይመስሉ የነበር ሲሆን ሁሉም ማህደሮች የተለያዩ ርዕሶችን ይዘው ነበር የተደረደሩት፡፡ ማህደሮቹ ወደ ተደረደሩበት ግድግዳ እየተጠጋሁ ስመጣ “የወደድኳቸው ልጃገረዶች” የሚል ርዕስ ያለው ማህደር ቀልቤን ሳበው፡፡ ይህን ርዕስ የያዘውን ማህደር በመግለጥ ካርዶቹ ላይ የተጻፉትን ማንበብ ጀመርኩ፡፡ በካርዶቹ ላይ ተጽፈው የነበሩትን ስሞች አውቃቸው ስለነበር ደንግጬ በፍጥነት ማህደሩን ዘጋሁት፡፡
ከዛም ማንም ምንም ሳይነግረኝ የት እንደምገን ተገነዘብኩ፡፡ ይህቺ ማህደሮች የታጨቁባት ሕይወት አልባ ክፍል የእኔም ሕይወት ተመዝግቦ የተቀመጠባት ‘ማህደር ክፍል’ እንደሆነች ተረዳሁ፡፡ በዚህች ክፍል ውስጥ ላስታውሳቸው ከምችላቸው በላይ ትልቁም ይሁን ትንሹ እያንዳንዱ የሕይወት ክንዋኔዎቼ ተመዝግበው ተቀምጠዋል፡፡
አለፍ አለፍ እያልኩ የተለያዩ ማህደሮችን እያነሳሁ በውስጣቸው ተጽፎ የሰፈረውን ማንበብ ስጀምር መገረምና ጉጉት ከፍርሀት ጋር ውስጤን ሲወረኝ ተሰማኝ፡፡ ከማነባቸው ነገሮች አንዳንዶቹ ደስታን እና ጣፋጭ ትዝታን ሲያጭሩብኝ ሌሎች ግን ወደ ኋላዬ በመዞር ከበስተጀርባዬ የሚያየኝ ሰው ያለ እስኪመስለኝ ድረስ ሀፍረት እና ጸጸትን ይጭሩብኝ ነበር፡፡ “ወዳጆች” የሚል ማህደር “የከዳኋቸው ወዳጆች” ከሚል ማህደር አጠገብ ተቀምጦ ነበር፡፡
ማህደሮቹ ካደረኳቸው ተራ ነገሮች አንስቶ እስከ ተገለጡ ትልልቅ ክፋቶቼ ድረስ በተለያየ ርዕስ ተመዝግበው ተቀምጠው ነበር፡፡ “ያነበብኳቸው መጽሐፍት”፣ “የተናገርኳቸው ውሸቶች”፣ “ለሌሎች ሰዎች ያደረኳቸው ማጽናናቶች”፣ “የሳቅሁባቸው ቀልዶች” የሚሉ ሁሉ ይገኙ ነበር፡፡ “ወንድሞቼ ላይ የጮህኳቸው ነገሮች” የሚል ርዕስ ያለው አይነት ማህደሮችን ስመለከት የርዕሶቹ ትክክለኛነት በራሱ ያስቀኝ ነበር፡፡ እንደ “ቤተሰቦቼ ላይ ያኩተመተምኳቸው ነገሮች” አይነት ርዕስ ያላቸው ማህደሮች ደግሞ ምንም የማያስቁ ነበሩ፡፡ የተለያዩ ካርዶችን ባነበብኩበት ጊዜ ሁሉ ካርዶቹ ላይ ተጽፈው በነበሩት ዝርዝር ይዘቶች መደነቄን አላቆምኩም ነበር፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ከጠበኳቸው በላይ ካርዶች በአንድ ማህደር ውስጥ የነበሩ ሲሆን አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ተስፋ ካደረኳቸው ካርዶች ያነሱ ካርዶች ነበሩ፡፡
እነዚህን ማህደሮች ማየቴ ይህን ሁሉ ነገር አድርጊያለሁ ወይ ብዬ እንድገረም አድርጎኛል፡፡ በሀያ አመታት እድሜዬ እነዚህን በሺዎች ምናልባትም በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ካርዶችን ለመጻፍ የሚያስችል በቂ ጊዜ ነበረኝን? እያንዳንዱ ያየሁት ካርድ ግን ጊዜ እንደነበረኝ የሚያስረግጥ ነበር፤ ምክንያቱም እያንዳንዱ ካርድ በራሴ የእጅ ጽሁፍ የተጻፈ እና የራሴው ፊርማ ያረፈበት ነበር፡፡
“የሰማኋቸው ዘፈኖች” የሚል ርዕስ ያለበትን ዶሴ አውጥቼ ስመለከት የዶሴው ይዘት እየጨመረ ሲሄድ ይታወቀኝ ነበር፡፡ ካርዶቹ በጣም ተጠጋግተውና ተጠቅጥቀው ተቀምጠው የነበረ ሲሆን ከሁለትና ሶስት ሜትር በኋላ እንኳን የማህደሩውን መጨረሻ ማግኘት አልቻልኩም ነበር፡፡ እነዚህን ሁሉ ሙዚቃዎች ለማዳመጥ ባባከንኩት ጊዜ አፍሬ ማህደሩን ዘጋሁት፡፡
“የዝሙት ምኞት” የሚል ርዕስ ያለው ማህደር ጋር ስደርስ ሰውነቴን ሲቀዘቅዘኝ ተሰማኝ፡፡ የማህደሩን ትልቀት ላለማየት በትንሹ ሳብ አደረኩትና አንድ ካርድ ከውስጡ አወጣሁ፡፡ በላዩ ላይ ሰፍሮ የነበረውን ዝርዝር ይዘት ሳነብ በፍርሀት ተንቀጠቀጥኩ፡፡ እንዲህ አይነት አሳፋሪ ጊዜ ተመዝግቦ በመቀመጡ ሕመም ተሰማኝ፡፡
ድንገት ኃይለኛ ቁጣ በውስጤ ሲቀሰቀስ ታወቀኝ፡፡ “እነዚህን ካርዶች ማንም ማየት የለበትም! ማጥፋት አለብኝ!” የሚለው ሀሳብ ተቆጣጠረኝ፡፡ እንደ እብድ አድርጎኝ ማህደሩን ጎትቼ አወጣሁት፡፡ ምንም ትልቅ ቢሆንም አስብ የነበረው በውስጡ ያሉትን ካርዶች አራግፎ ማቃጠል ነበር፡፡ ነገር ግን ካርዶቹን ከማህደሩ ውስጥ አውጥቼ ወለሉ ላይ ለማራገፍ ስሞክር አንድም ካርድ ማውጣት አልቻልኩም፡፡ ካርዶቹን በእጄ በመያዝ ለመቀዳደድ ብሞክርም እንደ ብረት ጠንካራ የሆኑ በመሆናቸው ማንም ላደርግ አልቻልኩም፡፡
ተሸንፌ እና ተስፋ ቆርጬ ማህደሩን ወደ ነበረበት ቦታ መለስኩት፡፡ ግንባሬን ግድግዳው ላይ አስደግፌ በራሴ በማዘን በረጅሙ ተነፈስኩ፡፡ ድንገት ወደ ማህደሮቹ ስመለከት “ወንጌልን የሰበኩላቸው ሰዎች” የሚል ርዕስ የያዘ ማህደር አየሁ፡፡ የዚህ ማህደር እጀታ በአጠገቡ ካሉ ማህደሮች ደመቅ ያለ ሲሆን ምንም ያለተነካ በመሆኑ አዲስ ነበር፡፡ ይህን ማህደር ይዤ ስስበው ርዝመትዋ ከስምንት ሴንቲ ሜትር ያልበለጠች ትንሽዬ ሳጥን እጄ ላይ ወደቀች፡፡ በውስጥዋ የነበረው ካርድ ብዛት በአንድ እጄ ልቆጥረው የምችለው ነበር፡፡
ከዛም እንባ በአይኔ ላይ ግጥም አለና ማልቀስ ጀመርኩ፡፡ በጉልበቴ ተንበርክኬ ከሆዴ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ፡፡ አለቅስ የነበረው ከተሰማኝ ታላቅ የሀፍረት ስሜት የተነሳ ነበር፡፡ እንባ ያዘሉ አይኖቼ በማህደሮች የተሞላውን መደርደሪያ ተመለከቱት፡፡ ስለዚህ ክፍል ማንም ሰው በፍጹም ማወቅ የለበትም፤ ቆልፌ ቁልፉን መደበቅ አለብን ብዬ አሰብኩ፡፡
እንባዬን ከአይኔ እየጠራረኩ እያለ ድንገት አየሁት፡፡ ወይኔ፣ በፍጹም እሱ መሆን የለበትም፡፡ እዚህ ቦታ ካልጠፋ ሰው ኢየሱስ ይገኛል ብዬ ያየሁትን ማማን አቃተኝ፡፡
ማህደሮቹን እየከፈተ ካርዶቹን ሲያነብ በተስፋ መቁረጥ እመለከተው ነበር፡፡ ምን ይለኝ ይሆን የሚለውን ሳስብ ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ፡፡ ቀና ብዬ ፊቱን አተኩሬ ለማየት አቅም አጣሁ፡፡ ነገር ግን ከኔ በላይ ሀዘን እንደተሰማው ያስታውቅ ነበር፡፡ ሆን ብሎ መጥፎ መጥፎ የተመዘገበባቸውን ማህደሮች እያወጣ የሚያነብ መሰለኝ፡፡ እያንዳንዱን ነገር የሚያነበው ለምንድን ነው?
በመጨረሻ ዞር ብሎ በሀዘን ስሜት ተመለከተኝ፡፡ አስተያየቱ ንዴትን ሳይሆን ራሴን ዝቅ አድርጌ፣ ፊቴን በእጄ ሸፍኜ ድጋሚ ማልቀስ እንድጀምር አደረገኝ፡፡ ወደ እኔ መጣና በእጆቹ ትከሻዬ ላይ አቀፈኝ፡፡ ብዙ ብዙ ነገሮችን ማለት ሲችል ምንም ሳይናገር አብሮኝ አለቀሰ፡፡
ከዛም ብድግ ብሎ ወደ ማህደሮቹ ሄደ፡፡ ከአንዱ ጥግ ጀምሮ ማህደሮቹን እየመዘዘና እያንዳንዱን ካርድ እያወጣ የእኔን ስም እየሰረዘ በስሙ መተካት ጀመረ፡፡
“በፍጹም አይሆንም!” ብዬ በመጮህ በፍጥነት ቆሞ ወደ ነበረበት ቦታ ሄድኩ፡፡ ይዞት የነበረውን ካርድ ተቀብዬው በወቅቱ ማለት የቻልኩትን “በፍጹም አይሆንም” የሚለውን ቃል ደጋግሜ አልኩት፡፡ ስሙ በእነዚህ ካርዶች ላይ በፍጹም መጻፍ የለበትም ብዬ አሰብኩ፡፡ ነገር ግን በደማቅና የሚያምር ቀይ ቀለም የእኔ ስም ጠፍቶ የእርሱ ስም ተተካ፡፡ በደሙ ነበር የተጻፈው፡፡
በእርጋታ ካርዱን ከተቀበለኝ በኋላ በሀዘን የተሞላ ፈገግታን ፈገግ ብሎ ካርዶቹ ላይ ስሜን በስሙ መተካትና መፈረሙን ቀጠለ፡፡ እንዴት እንደሆነ በፍጹም ልረዳው ባልቻልኩት ፍጥነት የመጨረሻውን ካርድ ፈርሞ ማህደሩን በቦታው አስቀምጦ አጠገቤ መጥቶ ሲቆም አየሁት፡፡ እጁን ትከሻዬ ላይ አድርጎ “ተፈጸመ” አለ፡፡
ተንስቼ ቆምኩና እየመራኝ ከክፍሊቱ ወጣን፡፡ በክፍሊቱ በር ላይ ምንም ቁልፍ አልነበረም፡፡ ነገር ግን ገና የሚጻፍባቸው ብዙ ባዶ ካርዶች ነበሩ፡፡
*****
እግዚአብሔር ሕይወትህን እንዴት እንደሚመለከተው አስበህ ታውቅ ይሆን? “እኔ እላችኋለሁ፥ ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል” (ማቴዎስ 12፥36)፡፡ ለራሳችን ታማኞች ብንሆንና ባንዋሽ ደጋግመን በሀሳባችን እና በድርጊቶቻችን ኃጢአት መስራታችንን በሀዘንና በጸጸት እናምናለን፡፡ እኛም በሚስጥር ስላሰላሰልናቸው ሀሳቦች እና ስለሰራናቸው ስራዎች ማፈራችን አይቀርም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በሮሜ 2፥16 ላይ “እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ……..በሰው ዘንድ የተሰወረውን በሚፈርድበት ቀን ይሆናል” ይላል፡፡ ሐዋርያው ጴጥሮስ “እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ……..ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም” (የሐዋርያት ሥራ 3፥19) ብሎ ሰብኳል፡፡ ኃጢአትህ በኢየሱስ ተደምስሶለሀል ነው ወይንስ ዛሬም ያሳድድሀል?
ነጻ መውጣት ትፈልጋለህን? ያለፈው ሕይወት ዘመንህ የሀሳብ እና የድርጊት ኃጢአት ሸክም ከብዶብሀልን? ኃጢአቶቻችን የልባችን እና የሕይወታችን ከባድ ሸክም ናቸው፡፡ “ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም” (1ኛ ዮሐንስ 1፥8)፡፡ “የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የዘላለም ሕይወት ነው” (ሮሜ 6፥23)።
ኢየሱስ ዛሬም ምህረትን ያደርጋል፡፡ ወደ አለም የመጣውና ደሙን ያፈሰሰው ለኃጢአተኞች ሁሉ ነው፡፡ እግዚአብሔር አቅዶት የነበረው የመዳን መንገድ ተገልጥዋል፡፡ መዳን ትወዳለህን? “እንግዲህ ልጁ አርነት ቢያወጣችሁ በእውነት አርነት ትወጣላችሁ” (ዮሐንስ 8፥36) ፤ (መዝሙር 51)። ወደ ኢየሱስ አሁን ና! ተጸጽተህ ኃጢአትህን ሁሉ ተናዘዝ፡፡ “በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው” (1ኛ ዮሐንስ 1፥9)። ኢየሱስ ከእርሱ ጋር እርካታ ወደ ሞላበት ሕይወት እንደሚመራህ እመነው፡፡ በእለት ተእለት የሕይወት እርምጃህ ምሪትን ይሰጥሀል፡፡